Update
ስለባቡሩ ግጭት‼
ኃይሎች የሚሄደውን አንድ ድንጋይ የጫነ ሲኖ ከአያት ወደ ጦር ሳሊተ ምህረት የሚሄደውን የከተማ ባቡር ጋር ተጋጭቷል።
ግጭቱ በባቡሩ የፉርጎ መገጣጠሚያ(የኋላና የፊቱ የሚገናኝበት) የደረሰ በመሆኑ ጉዳቱ ቀላል ሆኖ ተገኝቷል።በአንድ ሰው ላይ ነው መጠነኛ ጉዳት ያጋጠመው ሲሉ የአይን እማኞች ነግረውኛል።የሲኖው አሽከርካሪ ከመኪናው ወርዶ ማምረጡንም በቦታው የነበሩት ምንጮቼ አጋርተውኛል።እንኳንም ተሳፈሪ በሚበዛበት የባቡሩ ክፍል አደጋው አልተከሰተ።
በተያያዘ መረጃ
ዛሬ መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ረፋድ ላይ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ "የተባበሩት አደባባይ" አካባቢ በደረሰ ከባድ የትራፊክ አደጋ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ፣ በሦስት ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል።
እንደ ፖሊስ መረጃ፣ አደጋው የተከሰተው አንድ የ"አልያንስ" የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ቁልቁለት እየተጓዘ ሳለ ሁለት የቤት መኪናዎችን ገጭቶ አደባባዩ ላይ በመገልበጡ ነው። በአደጋው የፒካፕ መኪና አሽከርካሪ ወዲያውኑ ህይወቱ ሲያልፍ፣ ሁለት ተማሪዎች እና የቪትዝ መኪና አሽከርካሪ ለህልፈት የሚያሰጋ ጉዳት ደርሶባቸው በህክምና ላይ ይገኛሉ።
የአዲስ አበባ ፖሊስ አሽከርካሪዎች የመንገዱን ሁኔታ በማጤን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እያሳሰበ፣ ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝቷል።
#getahun mekonen
====================
አሁናዊ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን join በማድረግ በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ
👇👇👇
https://t.me/gate22522