2 months agoETB Aሰዎች ለምን በውሳኔዎቻቸው ይሳሳታሉ? ለምን ይሆን በአስተሳሰባቸው የማያስፈልግ ነገር የሚታየው? ለምንስ ነው ተፋልሶ የሚፈጽሙት? እነዚህንና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች እንድንጠይቅ የሚያደርገን የሰዎች አስተሳሰብ መጥራት በሚገባው ልክ አለመጥራቱ ነው። ስለ ተፋልሶና በአጠቃላይ ስለ አመክንዮ (ምክንያታዊነት) በማንበብና ጽሑፍ በማዘጋጀት ላይ እያለሁ በአንዳንድ ጽሑፎች የተፋልሶ ወይም በዐረፍተ ነገራዊ ብይን የሚታየው ስሕተት ምንጩ ያልጠራ የሰዎች አመለካከት እንደሆነ ማየቴ ይህንና ከዚህ በኋላ ተከታትለው የሚወጡትን መጻሕፍት እንድጽፍ አነሳስቶኛል። ሰዎች በሐይማኖት ማዕቀፍ ይሁኑ አይሁኑ፣ ጾታቸው ሆነ ዕድሜያች ተመሳሳይ ቢሆን ቢለያይ፣ የትምህርት ደረጃቸው ከፍ ያለ ቢሆን ዝቅ ቢል፣ ያደጉት አገራት ላይ ቢሆን በማደግ ላይ ያሉት ዜጎች፣ በአጠቃላይ የሰው ልጆች በሙሉ ለማለት በሚቻል መልኩ ያልጠራ አስተሳሰብ (bias) በየፈርጁ ይንጸባረቅብናል። የሺጥላ ይገዙ ...ይህ መጽሐፍ በጣም የሚያስታጥቀን (equip የሚያደርገን) ነገር የተዛቡ አመለካከቶችን እንድንረዳ ወይም እንድናውቅና ከእነሱ በምን መልኩ እንደምንወጣ የሚጠቁመን ወይም የሚያግዘን ነው። በተለይም ደግሞ ከተጠቂነት አስተሳሰብ ወይም እስራት ለመውጣት ይረዳል። ምክንያቱም ኮግኒቲቭ ዲስቶርሽን ራሱ እስር (የአእምሮ እስር) ነውና። ከዚህ ከማይታይ እስር ቤት ትልቁ ርምጃን የሚያሳየንና ተስፋን የሚሰጠን መጽሐፍ ነው፤ እኔ በጣም ወድጄዋለሁ አንባቢያን እንደሚወዱት ተስፋ አለኝ፤ ብዙ የተማርኩበት ነውና አንብቡት! ጸሐፊውን እንዲያሳትመውና ለብዙ ሰዎች እንዲያደርስ መምከሬም ለዚህ ነው፤ አንብባችሁ ተወያዩበት!” ትእግሥት ዋልተ ንጉሥ፣ የምን ሆኛለሁ? መጽሐፍ ጸሐፊ ...
2 months agoETB Aአራቱንም “የጠቅላይ ሚንስቴር ዶ/ር አቢይ”መጸሐፍት በመደብራችን በተመጣጣኝ ዋጋ ያገኙታል። ጃዕፈር መጸሐፍት እዉነተኛ ቅናሽ 📞0911932088 0911125324
2 months agoETB Aየመጽሐፍ ፊርማ ስነርአት ። የፊታችን ቅዳሜ ግንቦት 8 " ርዕስ የለውም " የተሰኘው መጽሐፍ ደራሲ ኤሊያስ ሽታሁን መጽሐፉ ላይ የፊርማ ስነስርአት ለማድረግ ከእናንተ ጋር ቀጠሮ ይዟል ! ቦታው ለገሃር ተወልደ ሕንጻ ስር የሚገኘው ጃዕፈር መጻሕፍት መደብር !
2 months agoETB Aባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ዕውቅና የተሰጠውና በአዎንታዊ መልኩ የተጠቀሰው " ናሂሊ " የተሰኘው የናትናኤል ከበደ ኤትኔግራፊክ ይዘት ያለው ይህ መጽሐፍ በመደብሮቻችን ሁሉ ይገኛል !